አዲስ አበባ፣ (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብን ሁለት ተጫዋቾችን ማስፈረሙን አስታውቋል።
ኢትዮጵያ ቡና የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን አንበል እና የቀይ ባህር እግር ኳስ ክለብ ተጫዋች የነበረው እና የሴካፋ ሀገራት ውድድር ላይ የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች ተብሎ የተመረጠውን ሮቤል ተክለሚካኤል ማስፈረሙን ነው የገለፀው።
በተጨማሪም ለደደቢት እንዲሁም ለከፋ ቡና የተጫወተውን ናትናኤል በርሔን እንዳስፈረመ በክለቡ ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ ላይ ገልጿል።
ሁለቱ ተጫዋቾች እስከ ሰኔ 30 ቀን 2014 ዓ.ም የሚያቆያቸውን ስምምነት ከክለቡ ጋር ተፈራርመዋል።