World News

(ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መንግስት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኤርትራ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ በማንሳቱ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈ

Posted by: Semere Asmelash

Date: Wednesday, 14 November 2018

መንግስት በኤርትራ ላይ ተጥሎ የነበረው ማዕቀብ በመነሳቱ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 14 ፣ 2018 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መንግስት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኤርትራ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ በማንሳቱ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈ።

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 5 ፣ 2011 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መንግስት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኤርትራ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ በማንሳቱ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈ።

የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ ተመድ በኤርትራ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ በማንሳቱ ለኤርትራ መንግስትና ህዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቱን አስተላልፏል።

ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ መንግስት በ2002 ተጥሎ የነበረው ማዕቀብ እንዲነሳ ጥያቄ ማቅረቡ የሚታወስ ሲሆን፥ ይህንን ጥያቄ ተከትሎም ተመድ ለሰጠው ምላሽ መንግስት ምስጋናውን አቅርቧል፡፡

እንዲሁም የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) አባል ሀገራት ማዕቀቡ እንዲነሳ ላበረከቱት አስተዋጽኦም አድናቆቱን ገልጿል፡፡

የማዕቀቡ መነሳት በአፍሪካ ቀንድ ለሚታየው መረጋጋትና ሰላም ዘለቄታዊነት ብሎም የቀጠናውን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር የላቀ ሚና ይጫወታል ተብሏል፡፡

መንግስት የማዕቀቡ መነሳት በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል በአዲስ መልክ የተጀመረውን የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ባህላዊ ትስስር የበለጠ እንደሚያጠናከረውም አስታውቋል።

በመጨረሻም የኢትዮጵያ መንግስት ለቀጠናው ሰላም፣ ልማትና ትብብር ከኤርትራና ከሌሎች ጎረቤት ሀገራት ጋር አብሮ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑንም የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ አመላክቷል።


ተመድ ኤርትራ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ አነሳ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 14፣ 2018 (ኤፍቢሲ) የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክርቤት ኤርትራ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ አነሳ፡፡
 
የጸጥታው ምክር ቤት አባላት ዛሬ ባካሄዱት ስብሰባ ማዕቀቡን በሙሉ ድምጽ ማንሳታቸው ተገልጿል፡፡
 
ማዕቀቡ የተጣለው ከዘጠኝ ዓመታት በፊት እንደነበረ የሚታወስ ሲሆን፥ የኤርትራ መንግስት ለአልሻባብ ድጋፍ ያደርጋል በሚል ነበር ሊጣል የበቃው፡፡
 
በዚህም ምክንያት ተጥለው ከቆዩት ማዕቀቦች መካከል በመሳሪያ ዝውውር፣ በባለስልጣናት የጉዞ እገዳና ንብረት እንዳይቀሳቀስ የሚያግዱ ነበሩ፡፡
 
ከዚህ ቀደም የኤርትራ መንግስት የተጣለውን ማዕቀብ አስመልክቶ ባወጣው መግለጫው እስከአሁን ለተዳከመው ኢኮኖሚ ካሳ እንደሚገባው አስታውቋል፡፡
 
የጸጥታው ምክር ቤት ማዕቀቡን ሊያነሳ የበቃው በቀጠናው እየሰፈነ ካለው ሰላም ጋር ተያይዞ መሆኑን ተገልጿል፡፡
 
በተያያዘም የኢፌዴሪ መንግስት ለዘጠኝ ዓመታት ተጥሎ የቆየው ማዕቀብ በመነሳቱ ለኤርትራ ህዝብና መንግስት የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፏል፡፡



EmbassyMedia - ራብዓይ ግንባር!

Dehai Events