አዲስ አበባ ፣ ህዳር 14 ፣ 2018 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መንግስት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኤርትራ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ በማንሳቱ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈ።
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 5 ፣ 2011 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መንግስት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኤርትራ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ በማንሳቱ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈ።
የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ ተመድ በኤርትራ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ በማንሳቱ ለኤርትራ መንግስትና ህዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቱን አስተላልፏል።
ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ መንግስት በ2002 ተጥሎ የነበረው ማዕቀብ እንዲነሳ ጥያቄ ማቅረቡ የሚታወስ ሲሆን፥ ይህንን ጥያቄ ተከትሎም ተመድ ለሰጠው ምላሽ መንግስት ምስጋናውን አቅርቧል፡፡
እንዲሁም የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) አባል ሀገራት ማዕቀቡ እንዲነሳ ላበረከቱት አስተዋጽኦም አድናቆቱን ገልጿል፡፡
የማዕቀቡ መነሳት በአፍሪካ ቀንድ ለሚታየው መረጋጋትና ሰላም ዘለቄታዊነት ብሎም የቀጠናውን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር የላቀ ሚና ይጫወታል ተብሏል፡፡
መንግስት የማዕቀቡ መነሳት በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል በአዲስ መልክ የተጀመረውን የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ባህላዊ ትስስር የበለጠ እንደሚያጠናከረውም አስታውቋል።