Dehai News

(አማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት) ኤርትራውያኑ የዕቁብ ብራቸውን ከነወለዱ ተረከቡ

Posted by: Semere Asmelash

Date: Wednesday, 20 February 2019

Published on Feb. 20 2019

8:19
Amhara Mass Media Agency

ኤርትራውያኑ ከ21 ዓመት በላይ በአደራ የተቀመጠ የእቁብ ገንዘብ ተመለሰላቸው

ኤርትራውያኑ ከ21 ዓመታት በኋላ 48 ሺህ የዕቁብ ብራቸውን ከነወለዱ ባህርዳር ከተማ ካሉ ወዳጆቻቸው ተረክበዋል፡፡

በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል በተፈጠረው ችግር ምክንያት ከወዳዶጃቸው ጋር የገቡትን እቁብ ገንዘብ በአደራ ተቀምጦ ከ21 አመታት በኋላ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ዳግም ሰላም በመፈጠሩ የአደራ ገንዘባቸውን ባህርዳር ከተማ በአካል ተገኝተው ተረክበዋል፡፡

በባህርዳር ከተማ ከ30 ዓመታት በላይ የኖሩት ኤርትራዊያኑ አቶ ፀሀዬ ሀይሉ እና ባለቤታቸው በአገራቱ መካከል ሰላም ተፈጥሮ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ በመምጣታቸው ደስታቸውን ገልፀዋል፡፡

በሁለቱ አገራት መካከል ዳግም ሰላም ይመጣና ተመልሰው ከወዳጅ ዘመዶቻቸው እንደሚቀላቀሉ እምነታቸው እንደነበርም አቶ ፀሀዬ ገልፀዋል፡፡

አብመድ



EmbassyMedia - ራብዓይ ግንባር!

Dehai Events