Dehai News

(ዶይቸ ቬለ) የጀርመን ም/ቤት የኢትዮጵያና ኤርትራን መቀራረብ አወደሰ

Posted by: Semere Asmelash

Date: Friday, 18 January 2019

አውሮጳ/ጀርመን  ቀን 18.01.2019

የጀርመን ም/ቤት የኢትዮጵያና ኤርትራን መቀራረብ አወደሰ

ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ታሪካዊ የሰላም ስምምነት ከፈፀሙ ከመንፈቅ በኋላ የጀርመን ምክር ቤት ሁለቱ የምስራቅ አፍሪቃ ሃገራት ያሳዩትን ሰላማዊ ቅርርብ አወደሰ። ምክር ቤቱ ሐሙስ ምሽት ባካሄደው ስብሰባ በጠላትነት ይተያዩ የነበሩት ተጎራባቾቹ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ሰላም ለማስፈን የፈፀሙት ዉል ዋንኛ ርምጃ ነዉ ሲል አድንቋል።
The Associated Press

ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ታሪካዊ የሰላም ስምምነት ከፈፀሙ ከመንፈቅ በኋላ የጀርመን ምክር ቤት ሁለቱ የምስራቅ አፍሪቃ ሃገራት ያሳዩትን ሰላማዊ ቅርርብ አወደሰ። ምክር ቤቱ ትላንት ሐሙስ ምሽት ባካሄደው ስብሰባ በጠላትነት ይተያዩ የነበሩት ተጎራባቾቹ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ባለፈዉ የጎርጎሮሳዊዉ 2018 ዓመት በመካከላቸዉ ያለዉን ዉዝግብ ለማስወገድና ሰላም ለማስፈን የፈፀሙት ዉል ዋንኛ ርምጃ ነዉ ሲል አድንቋል። ሁለቱ ሃገሮች ኤርትራ በጎርጎረሳዉያኑ 1993 ዓ.ም. ነፃነትዋን እስክታገኝ ድረስ አንድ እንደነበሩ የጀርመኑ የዜና ወኪል «DPA» በዘገባዉ አስታዉስዋል። ኤርትራ ነፃነትዋን ከአገኘች ከአምስት ዓመት በኋላ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል በተቀሰቀሰዉ ጦርነት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መሞታቸዉን የጀርመኑ የዜና ወኪል ዘግቦአል። የጀርመን ምክር ቤት ትናንት ሃሙስ ምሽት ባደረገዉ ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት የጀመረዉን የለዉጥ ተሃድሶ እንዲቀጥልበት አበረታቶአል። ይህንኑ ተከትሎ የምክር ቤቱ አባላት የኤርትራ መንግሥት በሃገሪቱ የዴሞክራሲ ግንባታን ፈር እንዲቀድ ጠይቀዋል።  በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚመራዉ የኢትዮጵያ መንግሥት በሃገሪቱ የዴሞክራሲ ግንባታን ከጀመረ ወዲህ ከኤርትራ አሁንም በርካታ ሰዎች እየተሰደዱ መሆኑን የጀርመን የዜና ወኪል «DPA» ዘግቦአል።   

አዜብ ታደሰ 

ተስፋለም ወልደየስ 

የጀርመን ም/ቤት የኢትዮጵያና ኤርትራን መቀራረብ አወደሰ | አውሮጳ/ጀርመን ...




6ይ ክፋል: ማዕበል ስርሒት ፈንቅል - የካቲት 1990 - ሰነዳዊት ፊልም| sirihit fenkil 1990 - part 6 - ERi-TV Documentary

Dehai Events