ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ እና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እንቁጣጣሽን በቡሬ ግንባር በጋራ እያከበሩ ነው፡፡
ባሕር ዳር፡ መስከረም 01/2011 ዓ.ም(አብመድ) ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ ፣ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሁለቱ አገሮች መካከል የተፈጠረውን እርቅ ተከትሎ በኢትዮጵያና በኤርትራ ድንበር መካከል ተገኝተው የቡሬ ግንባር ይባል በነበረው ቦታ በጋራ ሆነው ከሁለቱ አገራት የሀገር መከላከያ ሰራዊቶች ጋር የአዲስ ዓመትን እያሳለፉ ይገኛሉ::
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ.ቤት ኃላፊ አቶ ፍጹም አረጋ በፌስቡክ ገጻቸው እንዳስታወቁት አሁን ላይ ሁለቱ መሪዎች በጋራ እንቁጣጣሽን እያከበሩ ነው፡፡