Ethsat.com: በኢትዮጵያ የተደረገው የካቢኔ ሽግሽግና ሹመት ህዝባዊ ተቃውሞውን አያስቆመውም ተባለ

From: Berhane Habtemariam <Berhane.Habtemariam59_at_gmx.de_at_dehai.org>
Date: Wed, 2 Nov 2016 01:04:03 +0100

በኢትዮጵያ የተደረገው የካቢኔ ሽግሽግና ሹመት ህዝባዊ ተቃውሞውን አያስቆመውም ተባለ

ኢሳት (ጥቅምት 22 ፥ 2009)

November 1, 2016

Watch.

ESAT DC Morning News Tue 01 Nov 2016

http://ethsat.com/2016/11/esat-dc-morning-news-tue-01-nov-2016/

ESAT Daily News DC Tue 01 Nov 2016

በአቶ ሃይለማሪያም አቅራቢነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተደረገው የካቢኔ ሹም ሽር በኢትዮጵያ ውስጥ እየታየ ያለውን ውጥረት እንደማይቀርፍ ተገለጸ።

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በአዲስ መልክ ያደራጁትን ካቢኔ መጽደቁን ተከትሎ አስተያየት የሰጡት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት፣ አሁን ህወሃት እየሄደበት ያለው መንገድ በፊት ሲያደርገው ከነበረው ምንም ልዩነት የሌለው እንደሆነ ለመገናኛ ብዙሃን አስረድተዋል።

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ ዶር መረራ ጉዲና ባለፈው ሳምንት ለቪኦኤ ሲናገሩ በኢትዮጵያ ውስጥ እየተከሰተ ያለው የፖለቲካ ቀውስ ሊለወጥ የሚችለው አዲስ ምርጫ በማካሄድ እንጂ አሁን በስልጣን ላይ ያሉትን ባለስልጣናት ቦታ መቀያየር እንዳልሆነ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት የካቢኔ ሚኒስትርነት ሹመት ባለስልጣናቱ ባስመዘገቡት ውጤት ተመዝነው እንዲቀጥሉ ወይም ደግሞ እንዲሸጋሸጉ ተደርጓል ቢልም፣  የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት በበኩላቸው ከዚህ በፊት የነበሩትን ባለስልጣናት ማሸጋሸግ ወይም ደግሞ በአዳዲስ የኢህአዴግ አባላት መተካት የኢትዮጵያ ህዝብ አንግቦ የተነሳውን የነጻነት ጥያቄ አይመልሰውም ሲሉ ገልጸዋል።

ዶ/ር መረራ እንዳሉት ባለፈው ሳምንት እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚፈልገው የገዢው ፓርቲ ከስልጣን ወርዶ አዲስ ምርጫ እንዲደረግ እንጂ አሁን በስልጣን ላይ ያሉት ባለስልጣናት እንዲቀያየሩ አይደለም ሲሉ ለቪኦኤ የእንግሊዝኛው ክፍል ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ የሚፈልገው ህወሃት/ኢህአዴግ እየተከተለ ያለው የፖሊሲ እንዲለወጥ እንጂ እንዲጠገን አይደለም ሲሉ አስረድተዋል።

በተመሳሳይ መልኩ የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆኑት ሰለሞን ተሰማ ለዚሁ ለቪኦኤ የእንግሊዝኛ አገልግሎት እንደተናገሩት የአቶ ሃይለማሪያም መንግስት የሚያደርገው የካቢኔ ሽግሽግና ሹመት በቂ አለመሆኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ የፈለገው ነጻነትን እንጂ የሰዎችን መቀያየር አይደለም ሲሉ አቶ ሰለሞን ተሰማ ለቪኦኤ አስረድተዋል።

እየሰራን ያለውን ላለፉት 25 አመታት የኢህአዴግን የስልጣን የበላይነት ለማብቃት እንጂ ጠጋግኖ እንዲቀጥል አይደለም ያሉት አቶ ሰለሞን፣ በኢህአዴግ ውስጥም ሆነ ከኢህአዴግ ውጭ ለውጥ እንፈልጋለን ማለታቸውን በቪኦኤ የእንግሊዝኛው አገልግሎት ላይ የሰፈረው ዜና ያስረዳል።

የአለም አቀፍ ማህበረሰብ የኢትዮጵያ መንግስት ሁሉን-አቀፍ የሆነ ንግግር እንዲካሄድ በተደጋጋሚ መጠየቁ አይዘነጋም። ሆኖም የኢትዮጵያ መንግስት ከተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ጋር ለመነጋገር ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል። ህወሃት/ኢህአዴግ በአዲስ ካቢኔ ያካተታቸው ባለስልጣናት አብዛኞቹ የኢህአዴግ ፓርቲ አባላት መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።

********************************************************************************

የኢትዮጵያ ጦር ከሶማሊያ ለቆ የወጣው በአገሪቱ በተከሰተው የፖለቲካ ቀውስ መሆኑን አልሸባብ ገለጸ

ኢሳት (ጥቅምት 22 ፥ 2009)

November 1, 2016

የኢትዮጵያ ጦር ከሶማሊያ ለቆ የወጣው በኢትዮጵያ ውስጥ በተፈጠረው የፖለቲካ ቀውስ እንደሆነ አልሻባብ ገለጸ። ሃሳን ያቁብ የተባሉ የአልሻባብ መሪ ፣ የኢትዮጵያ ጦር ከሶማሊያ ለቆ በመውጣቱ አልሸባብ ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶታል ሲሉ አፍሪካ ኒውስ ለተባለ ጋዜጣ መናገራቸው ተሰምቷል።

የአልሸባብ አስተዳዳሪ የሆኑት ሃሳን ያቆብ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከሶማሊያ የወጡት ኢትዮጵያ በተፈጠረው የውስጥ ችግር ነው ቢሉም፣  የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ የኢትዮጵያ ሰራዊትን ከሶማሊያ መውጣቱ በቅርቡ ከታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር ምንም ግንኙነት እንደሌለው፣ በደምብ የታሰበበትና ሃላፊነት የተሞላበት ውሳኔ ነው እንደነበር ማስረዳታቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ መንግስት ለሰራዊቱና ሌሎች ወጪዎችን መክፈል አይችልም ያሉት አቶ ጌታቸው፣ የአለም አቀፍ ማህበረሰብ የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርግ ከሆነ ኢትዮጵያ ጦር ወደሶማሊያ ተመልሶ ለመግባት እንደሚችል ከዚህ በፊት ለመገናኛ ብዙሃን አስረድተዋል።

ባሳለፍነው የጥቅምት ወር ብቻ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከሶስት ቁልፍ ወታደራዊ ይዞታዎች ለቀው የወጡ ሲሆን፣ የሶማሊያ ታጣቂ ሃይል አልሸባብ ሶስቱን ስፍራዎች ተቆጣጥሮ እንደሚገኝ አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በበኩሉ የኢትዮጵያ ጦር ከሶማሊያ ለቆ በመውጣቱ የሲቪሉ ማህበረሰብ አልሸባብ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች የሚሰሩ የእርዳታ ሰራተኞች ህይወት አደጋ ላይ እንደጣለ ገልጿል። አልሸባብ የሶማሊያ ክልሎችን መልሶ መቆጣጠሩ በእርዳታ አሰጣጥ ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ችግር ማስከተሉንም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል።

በመንግስት ሃይሎች ተይዘው የነበሩ አንዳንድ ቦታዎች አሁን በአልሸባብ እጅ ወድቀዋል ያለው ይኸው አፍሪካ ኒውስ ላይ የወጣው ዘገባ፣ የኢትዮጵያ መንግስት ወታድሮች ለቀው በመውጣታቸው ለእርዳታ ስራ አስቸጋሪ የነበሩ ቦታዎች አሁን የባሰ አስከፊ ሁኔታ ገጥሟቸዋል ብለዋል።

Received on Tue Nov 01 2016 - 20:04:03 EDT

Dehai Admin
© Copyright DEHAI-Eritrea OnLine, 1993-2013
All rights reserved