Ethsat.com: ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወታደሮችና ደህንነቶች በዋልድባ ቁጥጥር ሲያደርጉ መሰንበታቸው ታወቀ

From: Berhane Habtemariam <Berhane.Habtemariam_at_gmx.de_at_dehai.org>
Date: Fri, 8 Apr 2016 22:13:21 +0200

ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወታደሮችና ደህንነቶች በዋልድባ ቁጥጥር ሲያደርጉ መሰንበታቸው ታወቀ

April 8, 2016

መጋቢት ፴( ሠላሳ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የገዳሙ አባቶች እንደገለጹት መጋቢት 27 የተከበረውን የመድሃኒአለም በአል ተከትሎ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወታደሮችና ደህንነቶች በገዳሙ በመግባት ቁጥጥርና ክትትል ሲያደርጉ ሰንብተዋል፡፡ ሁሉም ደህንነቶች ትግርኛ ብቻ የሚናገሩ የህወሃት ደህንነቶች መሆናቸውን የሚናገሩት አባቶች፣ ከወልቃይትና ከጎንደር ወደ ገዳሙ የሄዱ ምእመናን ከቤተሚናስ መነኮሳት ጋር ምን አይነት ግንኙነት አላችሁ በማለት ሲያዋክቡዋቸው እና ሲከታሉዋቸው ሰንብተዋል፡፡ የወልቃይት ህዝብ ጥያቄ ያሰጋቸው የህወሃት ደህንነቶች፣ ገዳሙን በተለዬ ሁኔታ ቁጥጥር እያደረጉበት ነው፡፡

ከወልቃይት ፣ ከጠገዴ ፣ ከዳንሻ፣ ሁመራ፣ አርማጭና ቆላ ወገራ በወልቃይት መዘጋ አድርገው ወደ ገዳሙ የሚሄዱ ቤተክርስያን ሳሚዎችን፣ ዛሬማ ወንዝ ላይ በማስቆም ከፍተኛ ፍተሻ ሲያደርባቸው ሰንብቶአል፡፡

በተለይ ማይበልጣ አፋፍ ወይም ውዳሴ ማርያም በተባለው ቦታ እና ሶስት ምእራፍ ላይ ከ200 ያላነሱ ምእመናን በሃወሃት የደህንነት አባላት ፍተሻ ተደርጎባቸው ንብረታቸው በሙሉ እንደተወሰደባቸው አባቶች ለኢሳት ተናግረዋል፡፡ በዚህ አካባቢ ፍተሻ ሲያካሂዱና ዝርፊያ ሲፈጽሙ የሰነበቱት የህወሃት ታጣቂዎች 4 ወንዶችና አንድ ሴት ሲሆኑ፣ ሴቶች የአንገት ሃብላቸው ሳይቀር እየተቆረጠ ተወስዶባቸዋል፡፡

ህወሃት የአካባቢው ህዝብ ተገናኝቶ በወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ እንዳይመክር የቀየሰው ስትራቴጂ መሆኑን የሚገልጹት የአይን እማኞች፣ ገዳሙ ከዚህ ቀደም ከደረሰበት ከፍተኛ ጥቃት በተጨማሪ ከወልቃይት ጥያቄ ጋር በተያያዘም ሌላው የጥቃት ማእከል ሆኖአል፡፡

በአሁኑ ሰአት ህወሃት መላው የትግራይ ህዝብ በወልቃይት ጥያቄ ጉዳይ ከህወሃት ጎን እንዲቆም ቅስቀሳ እያደረገ ሲሆን፣ ህዝቡን ለግጭት የሚያነሳሱና አንዱን ብሄር ጠላት አድርጎ ለማሳየት የሚደረገው ጥረት ህወሃት ከደርግ ጋር በነበረው ጦርነት ወቅት ያደርግ ከነበረው ቅስቀሳ ጋር ተመሳሳይ ነው በማለት ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ወገኖች ይገልጻሉ፡፡

******************************************************************************************************

በአፋር መጪው ጊዜ እጅግ አስፈሪ ነው ተባለ

April 8, 2016

መጋቢት ፴( ሠላሳ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከ20 ሚሊዮን ያላነሱ ዜጎችን ለረሃብ አደጋ ያጋለጠው ድርቅ፣ በአፋር ከመቼውም ጊዜ በላይ ከፍቶአል፡፡ እናቶች በየሳምንቱ በሞትና በህይወት መካከል ያሉ ህጻናትን ይዘው ረጅም ርቅት ተጉዘው ህክምና ለማግኘት ይጥራሉ፡፡ ረሃቡ የከፋ መሆኑንና አለማቀፉ ማህበረሰብ ባይደርስ ኖሮ ከዚህም በላይ ሊሆን እንደሚችል የአይ ቲ ቪ ኒውስ ጋዜጠኛ ቦታው ድረስ በመሄድ ዘግቦአል፡፡

በአንድ የህክምና ማእከል ውስጥ የሚሰራ ዶ/ር እንዳለው፣ ህጻናቱ ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ በተለያዩ በሽታዎች ተጠቅተዋል፡፡ ከ400 ሺ በላይ ህጻናት ለከፍተኛ የምግብ እጥረት መጋለጣቸውን ዘጋባው አመልክቶአል፡፡

የአንድ አመቱ ህጻን ሙሃመድ እናት የሆኑት ወ/ሮ አስሊ ክሊኒኩን ለማግኘት 4 ሰአታት ያክል በእግራው ተጉዘዋል፡፡ ቤታችን ውስጥ ምንም የሚበላ ነገር የለም ይላሉ፡፡ እንስሳት አልቀዋል፤ ለህጻናቱ የሚሰጥ ወተት የለም፡፡

ሌላዋ የአንድ አመት ህጻን እናት በበኩሉዋ በምግብ እጥረት ሳቢያ ለልጁዋ ወተት ማምረት አቁማለች፤፤ እንስሳ በማለቃቸው ወተት የለም፣ ስጋ የለም፡፡ ሙሉ በሙሉ ከመንግስት በሚሰጠው ምግብ ብቻ እየኖርን ነው፡፡ ብላለች፡፡

የህጻን ሙሃመድ አብዱ እናት በበኩለዋ ያለእርዳታ ይህ አካባቢ በሙሉ መቃብር ሊሆን ይችል ነበር ብላለች፡፡ የመንግስ ሰራተኛ የሆነው የጤና ባለሙያ ሰለሞን አብርሃ ፣ ነዋሪዎቹ ወደ አካባቢያቸው በተመለሱ በ2 ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ተመሳሳይ ችግር ይገጥማቸዋል ብሎአል፡፡

ችግሩ ገና አለመቀረፉን የሚገልጸው ጋዜጠኛው፣ 1 ቢሊዮን 400 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ እርዳታ ይፈለጋል፡፡ ይሁን እንጅ አለም በተለያዩ ችግሮች በመወጠሩዋ እርዳታ ማግኘቱ ቀላል አይሆንም፡፡ ለኢትዮጵያኖች የራሃብ ወሮች፣ በተለይም ለአፋር ህዝብ እጅግ አስፈሪ ጊዜ እየመጣ ነው ጋዜጠኛ ጆን ሬይ ዘግቦአል፡፡

Received on Fri Apr 08 2016 - 16:13:22 EDT

Dehai Admin
© Copyright DEHAI-Eritrea OnLine, 1993-2013
All rights reserved