ሰበር ዜና… ዛሬም ቁስለኞች ወደ ትግራይ እየተጋዙ ነዉ!!

From: Semere Asmelash <semereasmelash_at_ymail.com_at_dehai.org>
Date: Tue, 14 Jun 2016 17:35:30 +0000 (UTC)

http://www.satenaw.com/amharic/archives/17164

ሰበር ዜና… ዛሬም ቁስለኞች ወደ ትግራይ እየተጋዙ ነዉ!!

By ሳተናው ድረ-ገጽ / in የዕለቱ ዜናዎች / on Tuesday, 14 Jun 2016 11:33 AM

በትግራይ ነጻ አዉጪዉ ቡድን የተለኮሰዉን የጦር ጸብ አጫሪነት ኤርትራ በቀላሉ አልተመለከተችዉም! በመሆኑም በኢትዮ ኤርትራ አዋሳኝ ድንበሮች ዙሪያ ከፍተኛ መጠን ያለዉና ዘመናዊ የሆነ ሰራዊት ማለትም የአየር ወለድና ባሕር ሐይል አጠቃላይ ፊቱን ወደ ትግራይ ነጻ አዉጪዉ ጦር በማዞር ለግዳጅ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን መረጃዎቻችን ተናግረዋል።

ወያኔ ጦርነቱ ጋብ ብሏል የሚል ማስተባበያ ቢስጥም በኤርትራ በኩል ከፍተኛ የሆነ የበቀል እርምጃ በመዉሰዱ የወያኔ የቦርደር ሆስፒታሎች በቁስለኛ ወታደሮች ከመጨናነቃቸዉ በተጨማሪ ሌሎች ቁስለኞች ዛሬም ወደ ትግራይ ሆስፒታል መወሰዳቸዉን ምንጮች አሳዉቀዋል።

በባሕር ላይ ዉትድርና እረጅም አመታትን በእስራኤልና በግብጽ ሲሰለጥኑ የነበሩ የኤርትራ ሰራዊቶችን ወደተፈለጉበት የጥቃት ወረዳ እንዲፈነጠሩ በሚያስችል የወደብ ከተማዎች ላይ እያሰማራ የሚገኘዉ የኤርትራ አየር ሐይል ጦርነቱን እጅግ የሚፈልገዉ ይመስላል ያሉት መረጃዎች አክለዉ እንደገለጹት ዘመናዊ የሮማኒያ፣ ሩሲያ፣ እስራኤል ሰራሽ የሆኑ የጦር ጀቶች ትንኮሳ በተደረገባቸዉ ስፍራዎች ላይ እያንጃበቡ መሆኑን ገልጸዋል።

ዝግጅቱ በወያኔ በኩልም የቀጠለ ሲሆን የትግራዩ ነጻ አዉጪ ቡድን በአየር ሐይሉ ላይ ባለዉ ጥርጣሬ ምክንያት እንቅስቃሴዎች ብዙም እንደማይታዩ ምንጮች ሲገልጹ አያይዘዉ የወያኔ ሰራዊት ይህን ጦርነት ሆን ብሎ ለፍተሻ እንዳደረገዉ እና ኤርትራ ድብቅ የዉጊያ ስልቶችን፣ሐይሎችን እና ብቃትን በሙሉ ባለማዉጣት ወታደራዊ መረጃዎቿን እንድትጠብቅ አሳስበዋል።

ዜና በልዑል አለሜ
Received on Tue Jun 14 2016 - 13:35:31 EDT

Dehai Admin
© Copyright DEHAI-Eritrea OnLine, 1993-2013
All rights reserved