Ethsat.com: በጎንደርና ባህርዳር ከተሞች ለ6 ቀናት የሚቆይ የስራ ማቆም አድማ ተጀመረ

From: Berhane Habtemariam <Berhane.Habtemariam59_at_gmx.de_at_dehai.org>
Date: Tue, 20 Sep 2016 01:10:01 +0200

በጎንደርና ባህርዳር ከተሞች ለ6 ቀናት የሚቆይ የስራ ማቆም አድማ ተጀመረ

ኢሳት (መስከረም 9 ፥ 2009)

September 19, 2016

Watch these News:

Breaking News September 19, 2016

http://video.ethsat.com/?p=28550

ESAT Daily News Amsterdam September 19, 2016

http://video.ethsat.com/?p=28569

የጎንደርና ባህርዳር ከተማ ነዋሪዎች ለሶስተኛ ጊዜ ለስድስት ቀን የሚቆይ የስራ ማቆም አድማ ሰኞ ጀመሩ።

የስራ ማቆም አድማ መጀመሩን ተከትሎ በሁለቱ ከተሞች የሚገኙ አብዛኛቹ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ስራ ማቆማቸውንና አድማው ነዋሪው ያለውን ተቃውሞ በተከታታይ ለማሳየት ያለመ መሆኑን ነዋሪዎች ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አስረድተዋል።

በባህርዳር ከተማ ሰፍረው የሚገኙ የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች በቀበሌ 11 እና 13 አገልግሎት መስጫ ተቋማት በሃይል እንዲከፍቱ ሙከራን ቢያደርጉም የንግድ ባለቤቶች ፈቃደኛ ሳይሆኑ መቅረታቸውን እማኞች ገልጸዋል።

በከተማዋ ስብሰባን እያካሄዱ የሚገኙ የብሄረ-አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብዓዴን) አመራሮች ሰኞ ከሰዓት በኋላ የከተማ ሽማግሌዎች በጉዳዩ ዙሪያ እንዲመክሩ ለማድረግ ጥሪ ሲያቀርቡ እንደነበር የከተማዋ ነዋሪዎች አስታውቀዋል።

በተመሳሳይ ሁኔታም በጎንደር ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች ሰኞ የጀመሩትን የስድስት ቀን የስራ ማቆም አድማ ተከትሎ ከተማዋ ከእንቅስቃሴ ውጭ ሆና መዋሏን ነዋሪዎች ከዜና ክፍላችን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አስረድተዋል።

የከተሞቹ ነዋሪዎች ለእስር የተዳረጉ ሰዎች በአስቸኳይ እንዲፈቱና መንግስት የሚፈፅመውን ግድያ በአስቸኳይ እንዲያቆም በመጠየቅ ላይ መሆናቸው ታውቋል።

በሃምሌ ወር በጎንደርና በባህርዳር ከተሞች የተጀመረውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ ከ50 የሚበልጡ ነዋሪዎች የተገደሉ ሲሆን፣ ቁጥራቸው በአግባቡ ያልታወቀ ነዋሪዎችም ለእስር መዳረጋቸው እማኞች ሲገልፁ ቆይተዋል።

ሰኞ ለሶስተኛ ቀን የተጀመረው የስራ ማቆም አድማ ለእስር የተዳረጉ ሰዎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ ከመጠየቁ በተጨማሪ ነዋሪዎች አሁንም ድረስ በመንግስት ላይ ያለውን ተቃውሞ ለማሳየት ያለመ መሆኑን ከኢሳት ጋር ቃለምልልስን ያደረጉ ነዋሪዎች አስረድተዋል።

Received on Mon Sep 19 2016 - 17:49:06 EDT

Dehai Admin
© Copyright DEHAI-Eritrea OnLine, 1993-2013
All rights reserved