Ethsat.com: ህወሃት የበላይነት የሚመራው መንግስት በብሄረሰቦች መካከል መቃቃር እንዲፈጠር ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው ተነገረ

From: Berhane Habtemariam <Berhane.Habtemariam_at_gmx.de_at_dehai.org>
Date: Fri, 12 Aug 2016 01:06:54 +0200

ህወሃት የበላይነት የሚመራው መንግስት በብሄረሰቦች መካከል መቃቃር እንዲፈጠር ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው ተነገረ

August 11, 2016

ኢሳት (ነሃሴ 5 ፥ 2008)

Watch this news:

http://video.ethsat.com/?p=27027

http://video.ethsat.com/?p=27032

ESAT Efeta 09 Aug 2016

http://video.ethsat.com/?p=26930

በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ሰላማዊ ሰልፈኞች በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ህዝባዊ ተቃውሞች በአገሪቷ ለተፈጠረው ቀውስ የህወሃትን አመራር ተጠያቂ ነው ቢሉም፣ ስልጣን ላይ ያለው የህወሃት ቡድን በበኩሉ ሰላማዊ ሰልፈኞቹ የትግራይ ህዝብን በጅምላ ኢላማ ያደረጉ ናቸው በማለት በሰላማዊ ሰልፈኞቹ ላይ ክስ እያቀረበ እንደሚገኝ በአሜሪካ አገር ዋሽንግተን ዲሲ የሚሰራጨው ናሽናል ፐብሊክ ሬዲዮ (NPR) የተባለ ጣቢያ በረቡዕ ስርጭቱ ገለጸ።

በኦሮሚያና በአማራ ክልል ህዝባዊ ተቃውሞ ሲያሰሙ የነበሩት ሰላማዊ ሰልፈኞች፣ በፌዴራል መስሪያ ቤቶች ጨምሮ ቁልፍ የስልጣን ቦታዎችን የሚቆጣጠሩትና የስራ ዕድል የሚያገኙት (የሚሰጣቸው) የህወሃት አባላት መሆናቸውን ገልጸው፥ የጸጥታና ደህንነት፣ ዋና ዋና የኢኮኖሚ ተቋማት ጭምር እንዲሁ በህወሃት ሰዎች ተጨምድደው መያዛቸውን የተለያዩ አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ሰሞኑን ዘግበዋል።

ባሳለፍነው ሳምንት በኦሮሚያ በተደረጉ ሰላማዊ ሰልፎች በአገሪቷ ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል እንዲኖር፣ የገበሬዎች መሬት ያለአግባብ እንዳይወሰድ፣ ፍትህ እንዲሰፍን፣ ራስን በራስ ማስተዳደር ጥያቄዎች መቅረባቸውን NPR በዘገባው አስታውቋል።

ከሳምንት በፊት በጎንደርና በባህርዳር “ወያኔ ከእንግዲህ አይገዛንም” ፣ “ወልቃይት አማራ ነው”፣ “በኦሮሚያ ክልል ያለው ግድያ ይቁም” ፣ “በመብታችን አንደራደርም” የሚሉ መፈክሮችን ሲያስተጋቡ የነበሩት ሰልፈኞች መንግስት በህዝቡ ላይ የሚያደርገውን አፈና እንዲያቆም መጠየቃቸው ይታወሳል።

በተመሳሳይ መልኩ ባለፈው ቅዳሜ በአዲስ አበባ ለተቃውሞ ሰልፍ የወጡ ሰላማዊ ሰልፈኞች፣ “ነጻነት እንፈልጋለን፣ የፖለቲካ እስረኞችን ይለቀቁ” በማለት መፈክር ሲያሰሙ እንደነበሩና፣ በመጨረሻም ሰልፉ በፖሊስ ሃይል መበተኑን ኢሳት ዘግቧል።ባለፈው ሳምንት አርብ ጀምሮ በኦሮሚያና አማራ ክልል ከተሞች ሰላማዊ ሰልፈኞች ሰልፉ እንዳይካሄድ በመንግስት የተላለፈን ውሳኔ በመጣስ አደባባ መውጣታቸውን ይታወሳል።

በኢትዮጵያ ውስጥ ፖለቲካ ዘውግ ነው፣ ዘውግ ደግሞ ክልል ነው ያለው የNPR ዘገባ፣ በዘውግ ላይ የተመረኮዘ አከላለል አወዛጋቢ ከመሆኑም ባሻገር ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎችም በዚህ በዘውግ የፖለቲካ መስመር እንዲደራጁ አድርጓቸዋል ብሏል። በመንግስት ላይ የሚቀርበው ማንኛውም ትችትም በዘውግ የፖለቲካ መስመር እንደሚፈረጅ የሬዲዮ ጣቢያው አትቷል።

በመሆኑም በዘውግ ፖለቲካ በምትናጥ አገር ውስጥ እየተከሰተ ያለውን ችግር መግለጽ አገሪቷን “የጦር አውድማ” አድርጓታል በማለት የዜና አውታሩ በአገሪቷ እየተከሰተ ያለውን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚና አስተዳደራዊ ችግሮችን በዘገባው ዳስሷል።

በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች በከፍተኛ ሁኔታ እየተቀጣጠለ ያለውን ህዝባዊ ንቅናቄና የኢህአዴግ/ህወሃት አመራር እየወሰደ ያለውን የጅምላ ግድያ እርምጃ ኤን ፕ አርን ጨምሮ ሌሎች አለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን በከፍተኛ ሁኔታ ሽፋን እየሰጡት ይገኛሉ። ቢቢሲ፣ አልጀዚራ፣ ዩናይትድ ፕሬስ ኢንተርናሽናል፣ ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ታይምስ፣ ዶቼ ቬለ፣ ሲ ኤን ኤን፣ ዋሽንግተን ፖስት፣ ሮይተርስ፣ ኸፊንግተን ፖስት፣ ቮይስ ኦፍ አሜሪካ፣ አሶሽየትድ ፕሬስ እና ሌሎች በርካታ የዜና አውታሮች በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ እምቢተኝነትን ከዘገቡት አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ይጠቀሳሉ።

የአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃንን ሰፊ ዘገባን ተከትሎም የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በሳምንቱ መገባደጃ በኦሮሚያና አማራ ክልሎች የተፈጸሙ ግድያዎችን በገለልተኛ አለም አቀፍ ታዛቢ ቡድን ማጣራት እንዲደረግበት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ውይይት በማካሄድ ላይ መሆኑን ረቡዕ ይፋ አድርጓል።

*****************************************************************************************

የመሬት ፖሊሲው ካልተሻሻለ ህዝባዊ ተቃውሞ ወደ ዕርስ በእርስ ግጭት ሊያመራ ይችላል ተባለ

August 11, 2016

ኢሳት ( ነሃሴ 5 ፥ 2008)

የኢትዮጵያ መንግስት የመሬት ፖሊሲው ላይ ማሻሻያ የማያደርግ ከሆነ በመካሄድ ላይ ያለው ህዝባዊ ተቃውሞ ወደ ዕርስ በእርስ ግጭት ሊያመራ ይችላል ሲሉ አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር መግለጻቸውን ሮይተርስ ሃሙስ ዘግቧል።

በሃገሪቱ በመስቀለኛ መንገድ ላይ ናት ሲሉ ለዜና አውታሩ የገለጹት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ የሆኑት ዶ/ር መረራ ጉዲና የኢትዮጵያ ህዝብ ገዢው የኢህአዴግ መንግስት ለ25 አመታት በፈጸመው ድርጊት መሰላቸታቸውን አስረድተዋል።

ባለፈው ሳምንት በአካባቢው ተካሄዶ በነበረ ተቃውሞ የወረዳው ነዋሪዎች መገደላቸውን ያወሱት ነዋሪዎቹ ህዝቡ የተነሳውን ጥያቄ ዕልባት እስኪያገኝ ድረስ ትግሉን ለመቀጠል እየተንቀሳቀሰ እንድሆነ አስታውቀዋል።

“ህዝቡ መብቱን በመጠየቅ ላይ እንደሚገኝ ያስታወቁት የፓርቲው አመራር፣ መንግስት የሃይል እርምጃውን አጠናክሮ የሚቀጥል ከሆነ ህዝባዊ አመጹ ወደ ዕርስ በዕርስ ጦርነት ሊያመራ እንደሚችል ያላቸውን ስጋት ለሮይተርስ አስታውቀዋል።

በሳምንቱ መገባደጃ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች በተወሰዱ የሃይል ዕርምጃዎች ግድያ ከተፈጸመባቸው ሰዎች በተጨማሪ በሺዎች የሚቆጠሩ ተጨማሪ ነዋሪዎች ለእስር ተዳርገው እንደሚገኙ አቶ መረረ ጉዲና ገልጸዋል።

አዲስ አበባ ከተማን ወደ ኦሮሚያ ክልል ለማስፋፋት የተያዘውን እቅድ ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል ከመሬት ባለቤትነት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች በነዋሪው ዘንድ መነሳቱ ይታወሳል።

ይኸው ህዝባዊ ጥያቄ በመንግስት በኩል ተቀባይነት የማያገኝ ከሆነና  በሃገሪቱ የፖሊሲ ማሻሻያዎች ተግባራዊ ካልተደረጉ በመካሄድ ላይ ያለው ተቃውሞ ወደ እርስ በዕርስ ግጭት ሊያመራ ይችላል ሲሉ የኦፌኮ አመራር መግለጻቸውን ሮይተርስ በዘገባው አስነብቧል።

በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰው ተቃውሞ በአሁኑ ወቅት ወደ ሌሎች ክልሎች መስፋፋቱን የተናገሩት አቶ መረራ ጉዲና ህዝቡ እራሱን በትብብር እያደረጀ እንደሚገኝ አክለው አስታውቀዋል።

ከመሬት ጋር በተገኛኘ ከወራት በፊት የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ጥያቄውንና አድማሱን በማስፋት መንግስት ሊቆጣጠረው ወደማይችለው ደረጃ በመሸጋገር ላይ መሆኑንም አመራሩ ከሮይተርስ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ገልጸዋል።

ገዥው ኢህአዴግ መንግስት ለአመታት ሲያካሄድ በቆየው የመሬት ማፈናቀል ድርጊት በርካታ ሰዎች ህይወታቸው ወደ ድህነት ማምራቱንና በሃገሪቱ ፍትህሃዊ ስርዓት አለመኖሩን አቶ መረራ ጉዲና በወቅታዊ የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ጉዳይ ጋር በተገኛኘ ቃለመጠይቅ አከለው አስረድተዋል።

Received on Thu Aug 11 2016 - 17:45:59 EDT

Dehai Admin
© Copyright DEHAI-Eritrea OnLine, 1993-2013
All rights reserved