Ethsat.com: አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ አገሪቱ ከባድ የህልውና አደጋ ከፊቷ ተደቅኗል አሉ ሌሎች ወገኖች ግን አደጋው ለኢህአዴግ ህልውና እንጅ ለኢትዮጵያ አይደለም ይላሉ

From: Berhane Habtemariam <Berhane.Habtemariam_at_gmx.de_at_dehai.org>
Date: Fri, 5 Aug 2016 00:00:15 +0200

አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ አገሪቱ ከባድ የህልውና አደጋ ከፊቷ ተደቅኗል አሉ ሌሎች ወገኖች ግን አደጋው ለኢህአዴግ ህልውና  እንጅ ለኢትዮጵያ አይደለም ይላሉ

August 4, 2016
Watch these:
Daily News
1. http://video.ethsat.com/?p=26610
2. http://video.ethsat.com/?p=26615

ESAT Special News Gonder August 04 2016

3. http://video.ethsat.com/?p=26600

ሐምሌ  ፳፰ ( ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በባህርዳር ሲካሄድ በሰነበተው የዲያስፖራ በአል ላይ የተገኙት ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ ኢትዮጵያ ከባድ የህልውና አደጋ እንደተደቀነባት ተናግረዋል።

የጠባብነትና የትምክህትነት አደጋ ከፊታችን እንዳለ ዛሬ ሳይሆን አስቀድመን አውቀናል ያሉት አቶ ሃይለማርያም፣ ይህ ደግሞ አገራችንን ወደ ማትመለስበት የብሄር ግጭት አደጋና የእርስ በርስ ጦርነት ይከታታል ሲሉ ገልጸዋል። ሁላችንም ይህን ጠባብነትና ትምክት ተረባርበን ካላስቆምነው እስከዛሬ የተጓዝንበትን ሁሉ የሚያበለሽ አደገኛ የሆነ ክስተት መሆኑን አብራርተዋል።

አቶ ሃይለማርያም በኦሮምያና በአማራ ክልሎች የሚካሄዱ ህዝባዊ ተቃውሞዎች የመንግስትን ህልውና እየተፈታተኑ መምጣቱን በይፋ ያመኑ የመጀመሪያው የኢህአዴግ ባለስልጣን አድርጎአቸዋል። ህወሃት/ ኢህአዴግ በአሮምያ የሚካሄደውን እንቅስቃሴ በጠባብነት ሲፈርጅ በአማራ የሚካሄደውን እንቅስቃሴ ደግሞ በትምክት የፈርጀዋል። አብዛኛውን የኢትዮጵያ ህዝብ በቁጥር የሚወክሉት ሁለቱ ብሄሮች ተቃውሞአቸውን በጋራ እያሰሙ ባሉበት ወቅት   የኢትዮጵያን ህልውና አደጋ ውስጥ ሊጥሉት ነው ብሎ መናገር መሬት ላይ እየሆነ ያለውን ካለመረዳት ወይም የኢትዮጵያን አንድነት አስጠብቃለሁ በሚል ስም ጭፍጨፋ ለመፈጸም መዘጋጀታቸውን የሚያመለክት ነው ሲል ዘጋቢያችን አስተያየቱን አስፍሯል።

በአማራ እና በኦሮምያ ክልሎች የሚካሄደው ተቃውሞ በአርባምንጭና አጎራባች ወረዳዎችም  ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

******************************************************************************

አዲስ አበባን ጨምሮ በኦሮምያ፣ ባህርዳርና ደብረታቦር የሚደረገውን የተቃውሞ ሰልፍ የተሳካ ለማድረግ ዝግጅቶች እየተካሄዱ ነው

August 4, 2016

ሐምሌ  ፳፰ ( ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፊታችን ቅዳሜ በዋና ከተማዋ አዲስ አበባን ጨምሮ በመላው ኦሮምያ፣ በባህርዳር ከተማ እና በደብረታቦር ከተማ የተለያዩ የመብት ጥያቄዎችን የሚያቀነቅኑ የተቃውሞ ሰልፎች ይደረጋሉ። በእነዚህ ሰልፎች ላይ የህወሃት አገዛዝ እንዲያበቃ ጥሪ ይቀርባል። ሰልፉ በኦሮምያ የደረሰውን ጭፍጨፋ እንዲሁም የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ምንነት የኮሚቴ አባላት መታሰራቸውን ያወግዛል።

በኦሮምያና በባህርዳር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሰልፉን ቀን በጉጉት እየጠበቁት መሆኑን ይናገራሉ። አንድ  በባህርዳር ከተማ የሚኖር  ህዝቡ ብሶታል፣ ድምጹን የሚገልጽበት መድረክ አጥቶ ቆይቷል፤ አሁን አጋጣሚው ጥሩ በመሆኑ አንቀርም” ብሎአል።

በምእራብ አርሲ ነዋሪ የሆነው ግለሰብም ፣ ህዝቡ ሰልፉ ቢከለከልም ቢፈቀድም ድምጹን ለማሰማት ዝግጁ ነው ይላል። ህዝቡ የሚያጣው ነገር የለም የሚለው ግለሰቡ ፣ ኢትዮጵያ አንድነቷ ይፈራርሳል በማለት ገዢው ፓርቲ ተቃውሞ እንዳይደረግ የሚያደርገው ቅስቀሳ ባዶ መሆኗን፣ ኢትዮጵያ እነሱ እንደሚሉት አትፈርስም፣ ይህን ለመናገርም ጠንቋይ መሆን አያስፍልግም ብሎአል።

ከደቡብ ክልል አስተያየታቸውን የሰጡ አባት ደግሞ ተቃውሞው በመላው አገሪቱ አለመጠራቱ እንዳስቆጫው ገልጸው፣ በተለይ በባህርዳርና ደብረታቦር በሚካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ የመከላከያ ሰራዊቱ ከእናት እና አባቱ ጎን እንዲቆም ጠይቀዋል።

በአዲስ አበባ ነዋሪ የሆኑትና ቤታቸው በቅርብ የፈረሰባቸው ግለሰብ በአዲስ አበባ በሚደረገው ሰልፍ ለመሳተፍ መረጃ በስፋት እንዲሰጣቸው ጠይቀው፣ በባህርዳርና ደብረታቦር በሚደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ህዝቡ ድርጊቱን እንዲያወግዝላቸው ጠይቀዋል።

Received on Thu Aug 04 2016 - 16:39:19 EDT

Dehai Admin
© Copyright DEHAI-Eritrea OnLine, 1993-2013
All rights reserved