Zehabesha.com: በምዕራብ አርሲ የፌደራል ፖሊሶች ሬሳ አደባባይ ላይ ተጎተተ | 8 ወታደሮች ተገድለዋል ተብሏል

From: Berhane Habtemariam <Berhane.Habtemariam_at_gmx.de_at_dehai.org>
Date: Tue, 16 Feb 2016 15:11:12 +0100
TPLF POlice
 
(ዘ-ሐበሻ) ባለፈው አርብ በም ዕራብ አርሲ በአንድ የሰርግ ስነ ስርዓት ላይ የፌደራል ፖሊሶች ንጹሃን ዜጎችን ከገደሉ በኋላ በተነሳ የሕዝብ ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሎ ውሎ በዛሬው ዕለት 8 የፌደራል ፖሊሶች መገደላቸው ተሰማ:: ይህ የሟች ወታደሮች ቁጥር ሊጨምር ይችላል እየተባለም ነው::

ፖሊሶቹ ለተቃውሞ በወጡ የአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ጥይት ተኩሰው ከገደሉና ካቆሰሉ በኋላ ሕዝቡ በዚህ በመቆጣት በፌደራል ፖሊሶቹ ላይ የአጸፋ እርምጃ መውሰዱ ተሰምቷል:: በዚህም መሠረት በአደባባይ የወደቁት የፌደራል ፖሊሶች ሬሳ ሲጎተት እንደዋለና በየቦታው እንደወደቁም ተዘግቧል::

በም ዕራብ አርሲ አጄ ከተማ እንዲሁም በሻሸመኔ እና ሲራሮ ከተሞች ውጥረቱ እንዳለ ነው:: ሕዝብና የፌደራል ፖሊሶች ተፋጠዋል::

Received on Tue Feb 16 2016 - 09:11:13 EST

Dehai Admin
© Copyright DEHAI-Eritrea OnLine, 1993-2013
All rights reserved