Zehabesha.com: ሕወሓት የሚመራው የመከላከያ ሠራዊት አባላት ለኦሮሞ ሕዝብ ትግል ድጋፉን እየሰጠ ነው – ሰራዊቱ ድጋፉን ያሳየባቸው ፎቶዎች እየተለቀቁ ነው

From: Berhane Habtemariam <Berhane.Habtemariam_at_gmx.de_at_dehai.org>
Date: Thu, 4 Feb 2016 00:12:17 +0100

wetader 1

|

(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያ የተቀሰቀሰውን ሕዝባዊ አመጽ ተከትሎ ሕወሓት ከላይ የሚመራው የመከላከያ ሠራዊት አባላት ለኦሮሞ ህዝብ ትግል ድጋፋቸውን በመስጠት ላይ ይገኛሉ:: በሠራዊቱ ውስጥ በተለይ የኦሮሞና የአማራ ተወላጅ የሆኑ የጦር ሰራዊቱ አባላት አንድነት በመፍጠር ላይ እንደሚገኙ ከመከላከያ ምንጮች ያገኘናቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ::

በቅርቡ ሕብር ራድዮ ላይ ቀርቦ ቃለምልልስ የሰጠው ጀዋር መሐመድ “በሰራዊቱ ውስጥ የማደራጀት ሥራ ሰርተን ጨርሰናል:: በኦህ ዴድ ውስጥም እንዲሁም:: ሠራዊቱ መተኮስ ባለበት ወቅት ወደ ስር ዓቱ መተኮስ የሚችልበትን ሥራ ሰርተናል” ማለቱ የሚታወስ ሲሆን… ዛሬ በሶሻል ሚድያዎች እየተለቀቁ ያሉት ፎቶዎች እንደሚያሳዩትም የተለያዩ የሠራዊቱ አባላት እጃቸውን ወደላይ አድርገው በማጣመር ለኦሮሞዎቹ ትግል ያላቸውን አጋርነት በመግለጽ ላይ ናቸው::

wetader 2

ሕወሓት የሚመራው መንግስት በግድ ሕዝቡ እንዲቀበለው እያስገደደው የሚገኘውን ባንዲራም እየቀደዱ የሚያሳዩ ፎቶዎች ተለቀዋል::

ከመከላከያ ያገኘናቸው መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በአሁኑ ወቅት ውስጥ ውስጡን የኦሮሞና የአማራ ተወላጆች የሆኑ ወታደሮች በ ስር ዓቱ ግፍ በመንገብገብ የተደራጁ ሲሆን የሕወሃት ባለስልናት እርስ በ እርሳቸው እንዲከፋፈሉ ያዘጋጁትን ወጥመዶች እየበጣተሱ እንደሚገኙም ታውቋል::

wetader

በተለይ የኦሮሞና የአማራ ወታደሮች በአንድ ላይ ሕብረት መፍጠራቸው ያሰጋው ሕወሃት ሊያስተባብሩ ይችላሉ የሚላቸውን ወታደሮች በግድ የዓመት ፈቃድ እንዲወጡ እንዲሁም እያሰረም እየገመገመም እንደሚገኝ የዘ-ሀበሻ ምንጮች ገልጸዋል::

Received on Wed Feb 03 2016 - 18:12:17 EST

Dehai Admin
© Copyright DEHAI-Eritrea OnLine, 1993-2013
All rights reserved