Zehabesha.com: ከአማራ ክልል የመጡ ስደተኞች በአ.አ. ጎዳናዎች ላይ ካለመጠለያ ተበትነዋል – ልመና ጀምረዋል (ይናገራል ፎቶው)

From: Berhane Habtemariam <Berhane.Habtemariam_at_gmx.de_at_dehai.org>
Date: Wed, 6 Apr 2016 22:37:17 +0200

ከአማራ ክልል የመጡ ስደተኞች በአ.አ. ጎዳናዎች ላይ ካለመጠለያ ተበትነዋል – ልመና ጀምረዋል (ይናገራል ፎቶው)

የአይን እማኞች ዘገባ ከአዲስ አበባ

April 06, 2016

"ዘሕዝንን ምስልታት እዩ። ወንጀለኛ ምምሕዳር ወያነን ኣብ ስልጣን ዝርከቡ ኣባላቱን ኮራኹሩን ብሚልዮናት ዝቑጸር ሃብቲ ኢትዮጵያ ብዓመጽን ዓይኑ ብዘውጽኤ ዘረፋን ስርቅን ማሕፉዳኦም ከሕብጡ እንከሎዉ፣ ብሚልዮናት ዝቑጸር ውጹዕ ህዝቢ ኢትዮጵያ ግን ብጥሜትን ዓጸቦን ዝበልዖ ስኢኑ ካብ ዓድታቱ ገዝኡ ዓጽዩ ንከተማታትን ካሎኦትን ይስደድ ኣሎ፣ ኣብ ጽርግያታት ይልምን። ፋሽሽታዊ ጉጅለ ወያነ ብወንጀል ዝህደነሉን ዝዋረደሉን ግዜ ግን ውዒሉ ሓዲሩ ዘይተርፍ እዩ። ናይ ግዜ ሕቶ ጥራሕ እዩ"።

ብርሃነ ሃብተማርያም

ለዘ-ሐበሻ ዛሬ ከአዲስ አበባ የመጡ በርካታ ፎቶ ግራፎች እንደሚያሳዩት ከተማዋ ከአማራ ክልል በመጡ ስደተኛ የኔብጤዎች ተጥለቅልቃለች:: እንደፖለቲካ ተንታኞች አስተያየት በኢሕአዴግ የሥልጣን ዘመን ሁሉም ኢትዮጵያውያን እየደረሰባቸው ያለው ሰቆቃ ከፍተኛ ቢሆንም በአማራው ላይ ግን በጣም ለየት ያሉ ሰቆቃዎች እየተፈጸሙበት ነው:: የትግራይ ነፃ አውጪ መሪዎች ሳይቀሩ በአደባባይ “አማራው ጠላታችን ነው; እንዳያንሰራራ አድርገን ቅስሙን ሰብረነዋል” በሚናገሩባት በዚህች ሃገር አማራው ከተለያዩ ክልሎች ሰርቶ ያፈራውን ለቆ እንዲወጣ ሲደረግ; ሲገደል ንብረቱ ሲቃጠል ቆይቷል:: ከበደኖ እና ከአርባ ጉጉ ጭፍጨፋ ጀምሮ እስከ ቅርብ ጊዜው ጉራፈርዳ አማራው ሕይወቱን እየገበረ በሃገሩ ላይ እንደሁለተኛ ዜጋ ሲቆጠር ከቆየ ውሎ አድሯል::

ከአዲስ አበባ የመጡ ፎቶግራፎች እንደሚያሳዩት ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ከጎጃም; ከጎንደር እና ከወሎ የመጡ የአማራ ተወላጆች ቀያቸውን በስር ዓቱ በሚደርስባቸው ከፍተኛ በደል በመልቀቅ ወደ አዲስ አበባ እየተሰደዱ ነው:: በፎቶዎቹ ላይ እንደምትመለከቱት እናቶች አደባባይ ላይ ካለምንም መኖሪያና መጠለያ ተኝተዋል:: ልጆች ተበትነዋል:: አባቶች የሰው እጅ እያዩ ነው:: ይህ ሰቆቃ የሚያበቃው መቼ ይሆን? እነስብሃት ነጋ እንዳሉት “አማራውን እና ኦርቶዶክሱን እናጠፋዋለን” ፉከራ እየሰራ ይሆን? አስተያየት በመስጠትና መረጃውን በማስተላለፍ የአማራውን በደል እና ሰቆቃ በማሰማት ይተባበሩ::
amahara gebere

amhara gebere 3

amhara gebere 5

amhara gebere 6

amhara gebere1

ammhara gebere 4

Received on Wed Apr 06 2016 - 16:37:18 EDT

Dehai Admin
© Copyright DEHAI-Eritrea OnLine, 1993-2013
All rights reserved