Zehabesha.com: ሕወሓት እንደጥርስ መፋቂያ አንድ ጊዜ ተጠቅሞ የጣላቸውን የቀድሞ ወታደሮቹን እየሰበሰበ ነው

From: Berhane Habtemariam <Berhane.Habtemariam_at_gmx.de_at_dehai.org>
Date: Thu, 17 Mar 2016 23:07:08 +0100

ሕወሓት እንደጥርስ መፋቂያ አንድ ጊዜ ተጠቅሞ የጣላቸውን የቀድሞ ወታደሮቹን እየሰበሰበ ነው

March 17, 2016

mekele

(አቶ አሰገደ ገብረሥላሴ እንደዘገቡት) የህወሓት ነበር ታጋዮች ለመጭው  ቅዳሜ መጋቢት10/07/08 ዓ ም በህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ሥብሠባ ተጠርተዋል የዚህ ሥብሠባ  ኣለማ ኣልታወቀም::

ሕወሓት ደርግን ካሥወገዱ በኋላ ከ60 000 በላይ ወታደሮች ውስጥ 32 ሺህው ዲሞክራሢያዊ ጥያቄ በማንሣታቸው የህወሓት ኣማራርን ተግባራት በመቃወማቸው የተባረሩት ከዛ በኋላም በኣድልዎ በጎጠኝነት የተባረሩና በትውልድ ቀያቸው እንዳይኖሩም ከህዝብ ከወላጆቻቸው እንዲነጠሉ በማድረግ የተሣቃዩ ናቸው::

በተጨማሪ በጦርነት ኣካላቸው የጎደሉ 126 000 ወታደሮች ውሥጥ ከ4500 የማይበልጡ ጡሮታ ወይ በርድ የሚያገኙ ሌሎች ግን የተካዱ ነበሩ:: በድህነት ተሠቃዩ ሴት ታጋዮች ኣማራጭ ኣጥተው ወደ ዝሙት ሥራ ተሣማሩ:: የሕወሓት መሪዎች እና ተላላኪ ካድሬዎቻቸው ልዩ ዘር የሆኑባት አገር ሆነች::

እንግዲ የጅግኖች ካሣ ይህ ሆነ እና: የሕወሓት መሪዎች ግን ይህን ታጋይ የበረን ወታደር እንደ የጥርሥ መፋቅያ ተጥቀመው ይጥሉታል:: አንድ ጊዜ ደግሞ ሲጨንቃቸው የማያደርጉትን ተሥፋ በመሥጠት ይሰበስቡታል : ተጠቅመውም ይጡሉታል:: የኣሁኑ ሥብሠባም ላላቸው መከፋፈል ችግር ወደ ኣንዱ እንዳይወግኑ ሠብከው ወደ ጠባብነት ጎራ በማሠለፍ ሊጠቀሙባቸው ወይም ማሃል ሠፋሪ ለማድረግ ነው::

ይህን ለማሣካትም ጡሮታ እናደርግላችሁአለን ወይ ድጎማ እንሠጣችሁ ኣለን እያሉ ይሠብካሉ : በተግባር ግን ኣይውልም::

Received on Thu Mar 17 2016 - 18:07:08 EDT

Dehai Admin
© Copyright DEHAI-Eritrea OnLine, 1993-2013
All rights reserved