Facebook.com: ካብዝን ካብትን-የፌስቡክ ተቃዋሚዎች ኣብዮታዊ እርምጃ ይወሰድባቸዋል…!

From: Berhane Habtemariam <Berhane.Habtemariam_at_gmx.de_at_dehai.org>
Date: Fri, 11 Sep 2015 21:19:57 +0200

by Amdom Gebreslasie
September 11, 2015

የትግራይ ፌስቡክ ተጠቃሚዎች ኣብዮታዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው መሆኑ በኣባይ ወልዱ የሚመራው የህወሓት ኣንጃ ኣሳወቀ።
ኣንጃው ይህ ኣብዮታዊ እርምጃ እንደሚ ወስድ ያሳወቀው "12ተኛ ጉባኤ እንዴት ኣለፈ…?" የሚል ኣጀንዳ በየመንግስት መስርያ ቤቶች፣ ከመቐለ ከተማ ኑዋሪዎች፣ የክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ካድሬዎችና ኑዋሪዎች ውይይት እየተካሄደ ነው።

በመቐለ ማዘጋጃ ቤት ማክሰኞ 3/ 13/ 2007 ዓ/ም በኣቶ ተስፋኣለም ተወልደብርሃን (የመቐለ ከንቲባ)፣ ኣቶ ኣሰፋ ተገኝ ምክትል ከንቲባ የተመራ ስብሰባ የተካሄደ ሲሆን የህወሓት ጉባኤ ምን ይመስላል? የሚል ኣጀንዳ የተሰጠው ሲሆን የትግራዩ ኣንጃ በጉባኤው ወቅት በፌስቡክና በተባራሪ ወሬ የኣቶ ኣባይ ወልዱ ስም ክፉኛ ጠፍቷል በሚል እሳቤ የስም እዳሴ እያካሄዱ ነው።

1) ህወሓት ተከፋፍለዋል የሚል ወሬ ውሸት ነው።

2) ዳዊት ገ/ሄር በትግራይ መንግስት የሰጠው ቃለ መጠይቆች ውሸት ነው።

3) በፌስቡክ የሚሰራጩ መልእክቶች ውሸት ናቸው እንደታምኑ።

4) የጉባኤው ተሳታፊዎች ሚስጢር እንዲጠብቁ ማስጠንቀቅያ ቢሰጣቸው በቀጥታ ስርጭት ሊባል በሚችል ደረጃ በፌስቡክ ተዘግቧል።

5) በኣሁኑ ሰዓት ሁለት ዓይነት ጠላቶች ኣሉን። ፊት ለፊት ወጥተው የሚታገሉን እንደ ዓረና የመሰሉና በውስጣችን ሁኖው የሚታገሉን ክራይ ሰብሳቢ ሃይሎች( ከቅርብ ግዜ ጀምሮ በፌስቡክ ደረጃ ህወሓት መስለው ጀርባችን የሚወጉን ሃይሎች) ናቸው።

6) ኣባይ ወልዱ ሙስናን የሚጠየፍ፣ ታግሎ የሚያታግለን ጀግናና ብቁ መሪ ነው።

7) በፌስቡክ ተጠቃሚዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን።

8) ጉባኤው ፍፁም ዲሞክራሲያዊና በድል የተጠናቀቀ ነበር። ወዘተ የሚል ሃሳብ ወደ ተሳታፊዎች ኣቅርበዋል።

ተሰብሲቢዎቹ ታማኝ ካድሬዎችና ኣባላት በጥንቃቄ የተመረጡ ቢሆኑም ያቀረቡት ሃሳብና ተቃውሞ ግን ስብሰባው ላዘጋጀው ኣካል ኣስደንጋጭ ነበር።

ከተሳታፊው የቀረቡት ጥያቄዎች

ሀ) ኣባይ ወልዱ በጉባኤተኛ በ20ኛ(የፌስቡክ ማህበረሰብ ከክፍል 20ኛ ከዩኒት 1ኛ ብሎ የቀለደበት ነው።) ደረጃ ተመርጦ እያለ ሊቀ መንበርነት እንዴት ሊመረጥ ቻለ? እዚህ ላይ የጉባኤው ዲሞክራሲያዊነት የቱ ላይ ነው?

ለ) እነ ኣርከበ በድምፅ እንዲሳተፋ የተደረገበት፣ ለማእከላይ ኮሚቴ እንዳይወዳደሩ የተከለከሉበት ኣሰራር በየትኛው ደንብ ይገኛል?

ሐ) ዘመኑ ያመጣው የፌስቡክ ቴክኖሎጂ ህዝቡ እንዳይጠቀም እርምጃ እንወስዳለን ማለታቹ ግዜው የ21ኛ ክፍለ ዘመን መሆኑ ስላልገባቹ ነው? የሃይል እርምጃ ቴክኖሎጂው ምን ያህል ይቆጣጠረዋል ብላቹ ታስባላቹ?

መ) ኣቶ ዳዊትና ተቃዋሚ ድርጅቶች የሚነሱት ጉዳይ በመሬት ያለና ቀንተቀን የሚያጋጥመን ሃቅ ሁኖ ሳለ ኣትመኑት ውሸት ነው ማለታቹ ችግሮቹ ለመፍታት ኣቅም እንዳጠራቹ ኣያመላክትም ወይ? የሚሉትና ሌሎች ፈታኝ ጥያቄዎችና ሃሳቦች የቀረቡ ሲሆኑ የመቐለ ከንቲባና ምክትሉ የሚመልሱት ኣጥተው አንገታቸው ኣቀርቅረው በሃፍረት ከስብሰባው ወጥተዋል።

የተለያዩ የቢሮ ሃላፊዎች የመሩት የመንግስት ሰራተኞች ስብሰባዎች እየተካሄዱ ያሉ ሲሆኑ ዘመቻው ኣቶ ኣባይ ወልዱ የደረሰባቸው የይውረድልንና የስም ማጥፋት ዘመቻና የጠፋው ስም እንደገና የማደስ ስራ ተጠምደው ይገኛሉ።

የዚህ ዘመቻ ትኩረት ተደርጎ ያለው ፌስቡክና የፌስቡክ ተጣቃሚ ዎች ናቸው። ሰብሳቢዎች በተለያዩ መድረኮች ፌስቡክ ወጣቱ ትውልድ በኣሉታዊ ጎን እያበላሸው፣ የተቃውሞ መንፈስ እየበረዘውና እየበከለው በመሆኑ መንግስት እርምጃ ይወስዳል በማለት ኣዋጅ እያስነገሩ ይገኛሉ።

በክፍለ ከተሞች ከተካሄዱ ስብሰባዎች የሓወልቲ፣ ዓይደር፣ ሓድነትና ቐዳማይ ወያነ ተሰብሳቢዎች ከፍተኛ ውጥረት የተፈጠረ ሲሆን ባለ መግባባት ሊበተን ችለዋል።

ፌስቡክ ኣስመልክተው ከቀረቡት የኣቤታዊ እርምጃ ይወሰዳል ዛቻ ለትግራዩ ኣንጃ ደጋፊዎች የቀረበ ግምገማ " በቁጥር እኛ እንበዛለን፣ በኢንቴርኔት ኣክሰስ እኛ እንቀርባለን፣ ለነዚህ በጣት የሚቆጠሩ የፌስቡክ ተቃዋሚዎች መቃወምና ማሸነፍ ለምን ኣቃተን…?" የሚል ቁጭት ኣቅርበዋል።
እቺ ነገር መንግስቱ ሃይለማርያም " ትጥቅ ኣቀረብን፣ ስንቅ ኣቀረብን፣ ኣሁን የቀረን ልብ ማደል ነው። …… እንደ ወያነ ጠንክራቹ ኣትዋጉም ወይ…!" ብሎ ያደረገው የተስፋ መቁረጥና የስርዓቱ ማብቅያ ኣመላካች ንግግር በእጅጉ ይመሳሰላል።

የህወሓት ኣንጃዎች ክፍፍል ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን በነ ዶክተር ሰለሞን ዑንቋይ ለቀናት የፈጀ ሽምግልና ከመበተን እንደዳኑ ፀሓይ የሞቀ ሓቅ ለመካድ ቢሞክሩም ከህዝቡ የተሸፈነ ግን ኣልነበረም።
ኣሁን በመላ የትግራይ ወረዳዎች የኣባይ ወልዱ ስም ለመገንባት ከፍተኛ ጥረት በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የኣዲስ ኣበባው ኣንጃ ፊታውራሪ የሆኑት ዶክተር ደብረፅዮን በ12ኛ ጉባኤ የፌስቡክ የሚነሱ ሃሳቦች እንደ ትልቅ የሃሳብ ምንጭ ተቆጥሮ በጉባኤው ቀርቦ እንደተወያዩበትና ለጉባኤው እንደ ግብኣት እንደተጠቀሙበት ለቪኦኤ መግለፃቸው ይታወሳል።

የኣባይ ወልዱ ስም ለማጥፋት ኣገልግሎት ውለዋል የተባለው ፌስቡክና ተቃዋሚ ተጠቃሚዎች ኣቤታዊ እርምጃ ይወሰድባቸዋል።
የኢንቴርኔት ማእከላት ሊዘጉ ይችላሉ። ማነው ትግራይ ሰሜን ኮርያ ያላት ያው ውድድራችን ከሰሜን ኮርያ መሆኑ ነው።

ትግራይ ለምትገኙ ፌስቡክ ተጠቃሚዎች ኢትዮጵያውያን ኣብዮታዊ እርምጃ እንዳይወሰድባቹ የመንፈስ ዝግጅት ብታደርጉ እንመክራለን።

ነፃነታችን በእጃችን ነው…!

IT IS SO……!

************************************************************************************

በህወሓት ጉባኤ እንዲህ ሆነ
____________

የህወሓት ጉባኤ በሁለት ኣንጃዎች የስልጣን ሽኩቻ የጦዘ የጥሎ ማለፍ ፉክክር ተደሮጎበታል። የፖሊት ቢሮ ምርጫ ሲካሄድ የነደብረፅዮን ደጋፊ "ኣባይ ወልዱ ከሙስና የፀዳ ኣይደለም" የሚል ኣስተያየት ይሰጣል።
ኣባይም "እኔ በሙስና የምጠረጠር ኣይደለሁም። እርግጥ ነው ከገቢዬ የሰራሁት ሶስት ቤቶች ኣሉኝ። ልጆቼም ጥሩ በሚባል የግል ትምህርት ቤት ኣስተምራለው። የሌሎቻቹ ማእከላዊ ኮሚቴ ኣባላት ግን ልጆቻቹ ውጭ ኣገር በከፍተኛ ክፍያ እየከፈላቹ እያስተማራቹ ነው። በሙስና ጉዳይ የያንዳንዱ የማእከላዊ ኮሚቴ ኣባል ሰነድ በእጄ ይገኛል። ኣጣርተን ወደ ህግ እንቅረብ ካላቹ ዝግጁ ነኝ" በማለት እያንዳንዷ ባለ ስልጣን ክው ብላ ደርቃ እንድትቀር ኣድርጓል።
በጣም የሚያስገርመው ነገር ቢኖር ኣባይ ወልዱ በሙስና የማይመረረው እንደ ኣመራር በሶስት ቦታዎች ብቻ ፎቆች ሲሰራ የተቀረው በኣባይ ማስጠንቀቅያ ድምፁን ያጠፋው የማእከላይ ኮሚቴ ኣመራር ሁላ ምን ያህል ዘራፊ ቢሆን ነው?

የኢህኣዴግ ጉባኤው ካጠናቀቀ በሗላ በሰጠው መግለጫ ሙሰኞችና ክራይ ሰብሳቢዎች የመመንጠር ዘመቻ እንደሚያካሂድና በኣዲስ ኣበባ ዘመቻው እንደጀመረ እየገለፀ ነው።

ታድያ ኢህኣዴጎች ብቸኛው የኣብሮነታቸው መገለጫ የሆነው ሙስና ይታገላሉ ብሎ ማሰብ ሞኝነት ኣይደለምን? በትግራይ ያለሺው የኣዲስ ኣበባ ኣንጃ ደጋፊ፣ ቀስቃሽና ኣጨብጫቢ የነበርሺው ኣመራርም ኣባልም መንገድሺን ጥረጊ።
በህወሓት ቤት ሁሌ የሚታሰረው፣ የሚንገላታው ሙሰኛ ሳይሆን የተቃውሞ ድምፅ የሚያሰማ ሰው ነው።
ሙስናና ህወሓት የኣንድ ሳንቲም ሁለት ገፆች ናቸው።
ነፃነታችን በእጃችን ነው።
IT Is SO .…!

***********************************************************************************

ብኣዴን ዘኳድዳ ህወሓት..!
-------------------------

"..ሰሪሕካ ኣይትለውጠኒ.." ይብሉ ወለዲ ከምቲ ሎሚ ህወሓት ኣጋጢሙዋ ዘሎ ውድቀት ንከየጋጥሞምን ፈለማ ዝነበሮም ስብእና መሕዘናይ ብዝኾነ መልክዑ ከይልወጥ ንፈጣሪኦም እንትልምኑን።

ኣብ ዞባ ምዕራብ ትግራይ ኣብ መንጎ ክልል ኣምሓራን ትግራይን ዘሎ ሕቶ መሬት ይግበኣኒ ካብ እዋን ናብ እዋን እናተኻረረን ናብ ጎንፂ እናተሳገረን ይርከብ።

ኣብ ዋንነት መሬት ወረዳ ፀገዴን ኣብራሃ ጅራን ክልቲአን ክልላት ዘይምርድዳእ ዝተፈጠረ እንትኸውን ብፍላይ ኣብ 2007 ዓ/ም ብወገን ኣመሓደርቲ ክልል ኣምሓራ ዓብይ ህዝባዊ ምልዕዓል ዝፈጠሩልይን ክሳብ ዕጡቓት ምልሻታት ዘዝመትሉን ኣጋጣሚ ተፈጢሩን ሂወት ውን ዝጠፈአሉ ኹነታት ተፈጢሩ እዩ።

ነዚ ፀገም ንምፍታሕ ኣመሓደርቲ ክልቲአን ክልላት ብተደጋጋሚ ናብቲ ቦታ ብምኻድ ንምርድዳእ ዝፈተኑ እንትኾኑ ብወገን ብኣዴን ፀገዴ ወረዳ ናብ ክልሎም ክምለስ ዝሓተቱ እንትኾኑ ህወሓት ድማ "...ልዕሊ 60 ሺሕ ተጋሩ ይነብሩሉ እዮም.." ዝበሃል "..ኣብራሃ ጅራ ናብ ክልል ትግራይ ክካለል ኣለዎ.." ዝብል ሕቶ ቐሪቦም ነይሮም።

ብኣቶ በረኸት ስምኦን ዝምርሑ ብኣዴን ወነን ዓቕምን ናይ ሎሚ ህወሓት ብምግማት, ኣብ ውሽጣ ብምእታው ማለት "ብራኢ መለስ ኢና እንምራሕ" ንዝብሉ ጉጅለ ህወሓት ብምድጋፍን ኣብ ህወሓት ክፍፍል ክፍጠር ብምግባርን ክሳብ ዕጡቓት ምዝማት ዝበፀሐ ብክልል ኣምሓራ ፅዕንቶ ክበፅሕ ብምግባርን ናብ ወጥሪ ክትኣቱን ኣሽንኳይ ንኣብራሃ ጅራ ክትሓትት ንፀገዴ ውን ተገዲዳ ክትለቅቕ እናገበረታ ትርከብ።

በዚ መሰረት ኣብዚ ክረምቲ ክልቲኦም ኣመሓደርቲ ክልላት ዝተራኸቡ እንትኾኑ ህወሓት ልዕሊ 80% መሬት ኣብ ትሕቲ ክልል ትግራይ ይመሓደራ ዝነበራ ልዕሊ 20 ጣብያታት ንኣምሓራ ክልል ክተረክብ ክትውስን ተገዲዳ እያ። ዓቕሚን ወነን ዝኸሓዳ ህወሓት ይትረፍዶ ንኣብራሃ ጅራ ክትሓትት እቲ ምስኣ ዝነበረ ፀገዴ ክተርክብ ተገዲዳ ወሲና።

ኣቶ በረከት ስምኦን በቶም ብስም "ራኢ መለስ" ኣብ ዓንኬሎም ኣእቲዮም ዘሽከርክሩዎም ዘለዉ እኒ ኣቶ ቴድሮስ ሓጎስ፣ ኣባይ ወልዱ፣ ኣዜብ መስፍን ዘለዉሉ ጉጅለ ኣቢሎም ህወሓት ኣብ መዋጥር ክትኣቱ ብምግባር መሬት ፀገዴ ናብ ኣምሓራ ክልል ክፅምብሩ ኣብ ጫፍ በፂሖም ኣለዉ። እቲ ቦታ ድማ ሩባ ሞኮዞ ምላሽ እናተብሃለ ዝፍለጥ እዩ።

ሳራ ህወሓት ኣፀቢቖም ዝፈለጡ ብኣዴን ድማ "...ሩባ ኻዛ ምላሽ እንተዘይኾንና ኣይንቕበልን.." ብምባል ሓንጊዶም ይርከቡ።

እታ ጨጓር ከልቢ ህወሓት ሙሉእ ብሙሉእ መሬት ፀገዴ ክተረክብ ዝዓገታ ነገር እንተሃለወ እቲ ጉዳይ ብህዝቢ ተፈሊጡን ተወዓዊዑን ስለዘሎ ንምልክቱ ፀራሪጋ እንተሂባ ካብ ህዝቢ ዝመፅእ ተቓውሞ ንምክልኻል እዩ።

ኣቶ መለስ ዝመርሑዋ ዝነበረት ህወሓት ኣብ መረፃ 2002 ዓ/ም መድረክ ብግንባር ኣብ ዝጣመረሉ እዋን "...ስዬ ኣብራሃ ፀገዴን ወልቃይትን ንኣምሓራ ክንምልሰልኹም ኢና ኢሉ.." ብምባል ዘይተብሃለ ፃዕዳ ሕሶት መቐስቀሲ ተጠቒሞምሉ ነይሮ።

እቶም "መፈፀምቲ ራኢ መለስ ኢና" በሃልቲ ጉጅለ ኣብ ጉዳይ መሬት ብትኽክል መፈፀምቲ ራኢ መልስ ምኳኖም እናረጋግፁ ይርከቡ።

ኣቶ መለስ ውሳነ ቤት ፍርዲ "..ባድመ ንኤርትራ ትግባእ..." ኢሉ ኣብዝወሰነሉ እዋን "..ንሃቦም.." ዝብል ውሳነ ሂቦም ዝነበሩ እንትኾኑ ኩሉ ኢትዮዽያዊ ሆ ...ኢሉ ብምልዓሉን ካብታ ልዕሊኹሉ ዝፈትውዋ ስልጣኖም ከወግዶም ምኳኑ ምስ ተረድኡ መደናገርቲ ዝኾኑ "..ብዓል 5 ነጥቢ ናይ ሰላም እማመ.." ኢሎም ከውፅኡ ምግዳዶም ዝፍለጥ እዩ።

ነዚ ስዒቦም ኣቶ በረከት ድማ ንኤርትራውያን "...ባድመ ዘይተጠራጥር መሬት ኤርትራ እያ..." ብምባል ውግንነኦም ንዓድነኦምን ዓዲ ኣቦኦምን ምግባሮም ዝዝከር እዩ።

ኣቶ መለስ ነቶም ዓንዲ ህወሓትን ሓቀኛታት ደቂ ህዝቢ ዝኾኑ ምስ ብኣዴን ብምሕባር ክባረሩ ዝገበሩ እንትኾኑ ውፅኢቱ ድማ ህወሓት ስኒ ዘይብሉ ኣንበሳ ኮይና ክትተርፍ ገይሩዋ ይርከብ።

ህወሓት ኣብዚ ሐዚ እዋን ብኣዴን ብኽልተ መኹንዕ ዘኳድዳ ጉልበታ ዝጠለማ ምስኪን ውድብ ኮይና ትርከብ።

ህወሓት ኣብ ኣፍሞት እትርከብ ውድብ ምዃና ዘይረኣዮ ሰብ ይህሉዶ..?

ነፃነትና ኣብ ኢድና እያ።

IT IS SO..!

Received on Fri Sep 11 2015 - 15:19:58 EDT

Dehai Admin
© Copyright DEHAI-Eritrea OnLine, 1993-2013
All rights reserved