[dehai-news] Ethioforum.org: የህወሃት ቡድን ተከፋፈለ! Read in PDF: “የትግራይ ህዝብ ህወሓትን ቢጠላም በሌሎች ፓርቲዎች ላይ ጥርጣሬ አለው”

From: Berhane Habtemariam <Berhane.Habtemariam_at_gmx.de_at_dehai.org>
Date: Mon, 23 Sep 2013 13:29:43 +0200


የህወሃት ቡድን ተከፋፈለ!


(አብርሃም ደስታ – ከመቐለ)


 <http://www.hupso.com/share/> 23/09/2013

ህወሓት በአባይ ወልዱና ደብረፅዮን ቡድኖች በሁለት መከፈሉ ይታወቃል። ባለፈው የህወሓት የማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ የህወሃት እና ትግራይ ክልል ፕሬዘዳንት አባይና ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ተደርጎ የተሾመው ደብረፅዮን ጠብ በጣም በመክረሩ የተነሳ ሽጉጥ መማዘዛቸው ተሰምቷል። ሃይለማርያም ደሳለኝና በረከት ስምዖን ለማስታረቅ የሞከሩ ሲሆን ዉጤቱ አልታወቅም።

ይህ በ’ንዲህ እንዳለ የአባይ ቡድንም ሰሞኑ በሁለት ተከፍሏል፤ የአባይ ወልዱና የበየነ መክሩ። ከህወሓት ስብሰባ በኋላ የስልጣን ሽግሽግ ለማድረግ የተሞከረ ቢሆንም በየነ መክሩና ኪሮስ ቢተው ከስልጣናቸው ለመውረድ (ሓላፊነት ለመቀየር) ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ከአባይ ወልዱ ጋር ከፍተኛ አምባጓሮ ተፈጥሯል።

ኪሮስ ቢተው የትግራይ ግብርና ቢሮ ሓላፊና የኢንተርፕራይዞች የቦርድ ሰብሳቢ ነበር። አባይ ወልዱ ወደ ሌላ ቢሮ ሊቀይረው አስቦ ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል። የኢንተርፕራይዞች (ብዙ በጀት የሚመደብበት) ስልጣን ግን ቀምቶ ለአለም ገብረዋህድ ሰጥቶታል። ግብርና ቢሮም ለወዲ አዳል ታስቦ ነበር። ግን ጠብ ስለተነሳ አልተሳካም። በየነ መክሩም የንግድና ኢንዱስትሪ (የከተማ ልማት ጨምሮ) ስልጣን በእጁ ሲሆን አባይ ቢሮው ለሌላ ሊሰጠው ፈልጎ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ግን እስካሁን ውዝግብ ላይ ናቸው። በየነ መክሩ ወደ ሀገሩ (እስራኤል) የመሄድ ሓሳብ ይዟል።

የአባይ ቡድን በሁለት መከፈሉ (አባይና በየነ የሚመሩት) ማሳያ በትግራይ ክልል የዉሃ ሃብት ቢሮ አመራር አባላት የሁለቱ ቡድኖች ደጋፊዎች ተጣልተው እንደተደባደቡና አከባቢው እስካሁን በፌደራል ፖሊስ እየተጠበቀ መሆኑ ተረጋግጧል።

ስርዓት ሲበሰብስ እንዲህ ነው። ለማንኛውም ቸር ያሰማን።

 <http://ethioforum.org/wp-content/uploads/2013/09/tplf-chairman-abay-woldu-and-dep-chair-debretsion-gebremikael.jpg> ????? ?? ???? ??? ??? ?? ???? ??????

የህወሃት ሊቀ መንበር አባይ ወልዱ እና ምክትሉ ደብረጽዮን

 








image003.jpg
(image/jpeg attachment: image003.jpg)

Received on Mon Sep 23 2013 - 13:24:57 EDT

Dehai Admin
© Copyright DEHAI-Eritrea OnLine, 1993-2013
All rights reserved