| Jan-Mar 09 | Apr-Jun 09 | Jul-Sept 09 | Oct-Dec 09 | Jan-May 10 | Jun-Dec 10 | Jan-May 11 | Jun-Dec 11 | Jan-May 12 | Jun-Dec 12 |

[dehai-news] Ethsat.com: የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ ያቀረበውን የመነጋገርና የመታረቅ ጥያቄ ውድቅ አደረጉ

From: Berhane Habtemariam <Berhane.Habtemariam_at_gmx.de_at_dehai.org>
Date: Fri, 4 Jan 2013 00:48:36 +0100

የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ ያቀረበውን የመነጋገርና የመታረቅ ጥያቄ ውድቅ አደረጉ
News-
03.01.2013
ታህሳስ ፳፭(ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ከኤርትራ ቴሌቪዥን ጋር ቃል የተመላለሱት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ኤርትራ ስልጣን ላይ ካሉ ግለሰቦች መቀያየር ጋር የምታያይዘው አንዳችም ነገር የለም ካሉ በሆላ ዝንባሌው እራሱ ከኤርትራ ባህልና እሴት የሚቃረን መሆኑን ገልጠዋል::

እንነጋገር የሚለው አባባል ምንጩ ከየት እንደሆነ እንረዳልን ያሉት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ይህ አይነት አካሄድ ትኩረት ከማስቀየር በቀር ምንም አይነት ጥቅም እንደሌለውና ኤርትራም የምትገባበት ድራማ እንዳልሆነ አመልክተዋል::

የድንበር ኮምሽኑ ውሳኔ ተግባራዊ ላለመሆኑ የአሜሪካ መንግስት ተጠያቂ ነው ያሉት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እየተካሄደ መሆኑን ከሀገራቸው ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አስታውቀዋል::

ፕሬዚዳንቱ የአሜሪካ መንግስት በሀገራቸው ላይ የጣለውን መአቀብ በመቆቆም አንድነቱንና እድገቱን በማጠናከር መዝለቁንም በዚሁ ቃለምልልስ ገልጠዋል::


 

Received on Thu Jan 03 2013 - 21:21:33 EST

Dehai Admin
© Copyright DEHAI-Eritrea OnLine, 1993-2013
All rights reserved